Featured Post

10 መሠረታዊ የኮምፒውተሮቻችንን ደህንነት መጠበቂያ መንገዶች 10 Basic Ways to Secure Your Computer

Image
  10 መሠረታዊ የኮምፒውተሮቻችንን ደህንነት መጠበቂያ መንገዶች 10 Basic Ways to Secure Your Computer 1. ሁላችንም የጥቃት ዒላማ ውስጥ መሆናችንን መረዳት መቼም ቢሆን “የሳይበር ጥቃት እኔን አያጋጥመኝም" ብሎ አለማሰብ፡፡ ሁላችንም በግል እና በምናደርጋቸው የገንዘብ ዝውውሮች እንቅስቃሴያችን ወይም በነበረን መልካም ስም ላይ ተፅዕኖ የሚፈጥር አደጋ ሊያጋጥመን ይችላል፡፡ የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ የሁሉም ሰው ኃላፊነት ነው፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜም ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ 2. ለሶፍትዌሮች ወቅታዊ ዝመና ያድርጉ የኦፕሬቲንግ ሲስተሞቻችን /Operating System/ እና ፕሮግራሞቻችን የዘመኑ ሶፍትዌሮችን መጫን መሠረታዊ ነገር ነው፡፡ ሁልጊዜም የቅርብ ምርት የሆኑ የደህንነት ዝመናዎችን ማድረግ ጠቃሚ ነው፡፡ በተጨማሪም፡- • የመሣሪያዎትን ኦፕሬቲንግ ሲስተም ቀጥተኛ ዝመና /Automatic Update/ ላይ ያድረጉ፣ • ቀጥተኛ የደህንነት ዝመና በየጊዜው የሚያቀርቡ እንደ ክሮም ወይም ፋየር ፎክስ /Chrome or Firefox/ ያሉ የድረ-ገጽ ማፈላለጊያዎችን መጠቀም ይመከራል፣ • እንደ ፍላሽ፣ ሀርድ ዲስክ እና የመሳሰሉ ተንቀሳቃሽ መሣሪያዎችን ሲጠቀሙ ሁልጊዜም ወቅታዊ ዝመና የተደረገላቸው መሆናቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ 3. የፌሺንግ ጥቃት ሙከራዎችን ያስወግዱ የፊሺንግ ጥቃት የተለያዩ የማህበራዊ ምህንድስና መንገዶችን በመጠቀም የሚፈፀም ቋሚ ስጋት ሲሆን የሳይበር ወንጀሎች እንደ የይለፍ ቃል ባንክ መረጃዎች እና ክሬዲት ካርድ ያሉ ግላዊ መረጃዎችን የሚያጭበረብሩበት ነው፡፡ • የፊሺንግ ጥቃት ብዙውን ጊዜ በኢ-ሜይል አድራሻ፣ ከዚህ በተጨማሪም በስልክ፣ በመልዕክት መለዋወጫ ወይም በማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች የሚፈጸ...

በአዳማ ከተማ በ2 ቢሊየን ብር የኮንፈረንስና ኮንቬንሽን ማዕከል ሊገነባ ነው

በአዳማ ከተማ በ2 ቢሊየን ብር የኮንፈረንስና ኮንቬንሽን ማዕከል ሊገነባ ነው
********************************************************************


አዳማ ከተማን የኮንፈረንስና እና ኮንቬንሽን ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የአዳማ ከተማ አስተዳደር ገለጸ።
የከተማ አስተዳደሩ ከተማዋን የኮንፈረንስ እና ኮንቬንሽን ማዕከል ለማድረግ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ ነው የተገለፀው።
የማዕከሉ ዲዛይን ተሰርቶ የተጠናቀቀ ሲሆን ፥ዲዛይኑም የአካባቢውን ማህበረሰብ ባህል እና እሴት በጠበቀ መልኩ የተሰራ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አቶ መስፍን አሰፋ ተናግረዋል።
ከዚህ ባለፈም ማዕከሉ መንግስትን እና የአካባቢውን ባለሀብቶች በማሳተፍ የሚሰራ መሆኑ ነው የተገለፀው።
ዲዛይኑ ተሰርቶ እንደተጠናቀቀም ከባለሀብቱ ጋር ወይይት ተደርጓል ያሉት ከንቲባው፥ የማዕከሉ ግንባታ ፈርጀ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው አንስተዋል።
ግንባታው ከ3 እስክ 5 ዓመት ጊዜ የሚፈጅ ሲሆን፥የዘንድሮውን አመት ለዝግጅት በመያዝ በቀጣይ ወደ ግንባታ ለመግባት በትኩረት እንሰራለን ነው ያሉት።
ግንባታውን አጠናቆ ለመጨረስም 2 ቢሊየን ብር ስፈልጋል ያሉት ከንቲባው ፥ለግንባታው የሚያስፈልገው የ10 ሄክታር መሬት የማዘጋጀት ሂደቱም ተጀምሯል ብለዋል።
በሌላ በኩል በከተማዋ ከኢንቨስትመንት ጥያቄ ጋር ተያይዞ የሚነሳውን ቅሬታ መቅረፍም፥ በዚህ አመት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራበት ያለ ጉዳይ መሆኑን ነው ከንቲባው የተናገሩት።
ኤፍ ቢ ሲ እንደዘገበው ብዙ ጊዜ የከተማዋ አቅም እና የኢንቨስትመንት አማራጭ ላይ በቂ ዝግጅት ስለማይደረግ ባለሀብቱ የኢንቨስትመንት ፍቃድ ጠይቆ ምላሽ ሳያገኝ ለበርካታ አመታት መቆየቱ እና ይህም የተለያየ ቅሬታ መፍጠሩንም ከንቲባው አንስተዋል ።
የተጠራቀሙ ጥያቄዎችን ለመመለስ እና የዘርፉን ውስንነቶች ለመቅረፍም የከተማዋን አቅም እና የኢንቨስትመንት አማራጮች የመለየት ስራ እየሰራ ነው ብለዋል።
አሁን ላይ ለመስራት ከታሰበው የኮንፈረንስና የኮንቬንሽን ማዕከል አጋዥ የሆኑ ባለ አምስት ኮኮብ ሆቴሎች ለመስራት ፍቃድ የሚጠይቁ ባለሀብቶች በቅድሚያ የሚስተናገዱ መሆኑን ከንቲባው ጠቁመዋል።
**************************************************************************************************************

Comments

Popular posts from this blog

WHO IS FULL-STACK DEVELOPER & WHY MANY PROGRAMMERS FAIL?

10 መሠረታዊ የኮምፒውተሮቻችንን ደህንነት መጠበቂያ መንገዶች 10 Basic Ways to Secure Your Computer

Top 5 Ways To Protect You From Hackers Online 2020 Tips